

<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://eeu.gov.et/index.php/feed/am</id>
                                <link href="https://eeu.gov.et/index.php/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://www.eeu.gov.et) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-04-08T09:49:51+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[ከነዳጅ ማደያ ወደ ኃይል መሙያ ጣቢያ !]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/index.php/publication/detail/2191?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/index.php/2191</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>በአሁኑ ወቅት ዓለማችን ከነዳጅ ጥገኝነት ተላቃ ወደ ታዳሽ የኃይል ምንጮች የምታደርገው ሽግግር ከምንጊዜውም በላይ እየተፋጠነ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ሽግግር በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚደረገው ጥረት አካል ሲሆን፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) ደግሞ የዚህ ለውጥ ግንባር ቀደም ተዋናዮች ሆነው ብቅ ብለዋል። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር በዝምታ ከመመልከት ይልቅ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማበረታታትና በስፋት እንዲገቡ በማገድ ረገድ በአፍሪካ አህጉር ቀዳሚና አስደናቂ &nbsp;እርምጃ የወሰደች ሀገር ሆና ተመዝግባለች።&nbsp;<br>&nbsp;</p><p>ይሁን እንጂ ማንኛውም የቴክኖሎጂ ሽግግር ያለ ጠንካራ መሠረተ ልማት ዝግጅት ስኬታማ ሊሆን አይችልም። የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቁጥር መጨመር በራሱ ግብ ሳይሆን፣ "ተሽከርካሪዬን የት ቻርጅ አደርጋለሁ?" ለሚለው የተጠቃሚዎች ስጋት አስተማማኝ ምላሽ መስጠት የግድ ይላል። ይህንን እውነታ ታሳቢ በማድረግ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሀገሪቱን የነገ ጉዞ የሚወስን ስትራቴጂካዊ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።<br>&nbsp;</p><p>በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ ኮተቤ አካባቢ በ170 ሚሊዮን ብር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የተገነባው ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ ጣቢያ (EV Charging Station) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ፣ በሀገሪቱ የትራንስፖርት ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፋች ሆኗል። ይህ ጣቢያ ተራ የቴክኖሎጂ ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባ ነዳጅ ላይ ያላትን ጥገኝነት ቀንሳ በራሷ የተፈጥሮ ኃይል (በተለይም በሃይድሮ ፓወር) ለመጠቀም የጀመረችው ጉዞ ግዙፍ ማሳያ ነው።<br>&nbsp;</p><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዘመናዊ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህ እንቅስቃሴ የ"አረንጓዴ ኢኮኖሚ" ስትራቴጂን ከማገዝ ባለፈ፣"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" የተሰኘውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት የላቀ ሚና ይጫወታል። ተቋሙ በሀገሪቱ ብቸኛው የኃይል አቅራቢ እንደመሆኑ መጠን፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለማስፋፋት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የመሠረተ ልማት ግንባታውን በዋና ተግባርነት ይዞታል።<br>&nbsp;</p><p>እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ወደ 140 ሺህ የሚጠጉ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ቢሆንም፣ ከተሽከርካሪዎቹ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን የኃይል መሙያ ጣቢያዎች አለመሟላት ለተጠቃሚዎች ዋነኛ ፈተና ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ 32፣ እንዲሁም በሌሎች የክልል ከተሞች 8 በድምሩ 40 የቻርጂንግ ስቴሽኖችን ለመገንባት በከፍተኛ ፍጥነት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። &nbsp;</p><p>&nbsp;</p><p>በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሶስት ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ያደረገ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ሶስት ጣቢያዎች ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ። ተቋሙ በከተማ ደረጃ ብቻ ሳይወሰን፣ በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ በቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ ባቱ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ እና ሐዋሳ ከተሞች ላይ የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት እቅድ ይዟል። ለዚህም የሚያስፈልጉ 34 ፕሮጀክቶች ግብዓቶች፣ ትራንስፎርመሮች እና የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አስቀድመው ተዘጋጅተዋል።<br>&nbsp;</p><p>የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ በበላይነት በሚያስተናግደው የኢትዮ-ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር ላይ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን መጠቀም ለሀገር ያለው ጠቀሜታ እጅግ ከፍተኛ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር፣ በዚህ ስትራቴጂካዊ መስመር ላይ አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ለማሟላት እየሰራ ይገኛል። ይህም የትራንስፖርት ወጪን ከመቀነስ ባለፈ፣ በነዳጅ ግዢ የሚባክነውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመታደግ ያስችላል።<br>&nbsp;</p><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የገነባቸው የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች 24 ሰዓት የሚሰሩ ሲሆን፤ የኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም ባህልን ለማሻሻልና ከፍተኛ የኃይል ጭነት በማይኖርበት ጊዜ ደንበኞች ኃይል እንዲጠቀሙ ለማበረታታት በሚጠቀሙበት ጊዜ ላይ መሰረት ያደረገ ምክንያታዊ የቻርጅ ማድረጊያ ዋጋ እንዲተገበር ተደርጓል፡፡ ለአገልግሎቱ ተጠቀሚዎች ለአንድ ኪሎ ዋት ሶስት የክፍያ ዋጋ አማራጮች ቀርቧል።<br>&nbsp;</p><p>ይህ የዋጋ ተመንም፤ ከምሽቱ 4:00 እስከ ጠዋት 12:00 ሰዓት (Off-Peak)፦ ለአንድ ኪሎ ዋት (kWh) 14.85 ብር። ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 11:00 ሰዓት &nbsp;ለአንድ ኪሎ ዋት 16.57 ብር። ከቀኑ 11:00 እስከ ምሽቱ 4:00 እና ከጠዋቱ 12:00 እስከ 4:00 (Peak Hours)፦ ለአንድ ኪሎ ዋት 18.28 ብር ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። ይህ አሰራር ተጠቃሚዎች በሌሊት ቻርጅ በማድረግ ወጪያቸውን እንዲቆጥቡ ከማስቻሉም በላይ፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈጠርን ከፍተኛ ጫና ይቀንሳል።&nbsp;<br>&nbsp;</p><p>በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ተጠቃሚዎችን እርካታ ለማሳደግና ሀገራዊ የለውጥ እቅዶችን ለማገዝ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው። በኮተቤ ሳአሊተ ምህረት ፊት ለፊት እና ፒያሳ በቀድሞው የአገልግሎቱ ዋና መ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተጀመረው ይህ ዘመናዊ የኃይል መሙያ ጣቢያ፣ ለኢትዮጵያ ንጹህ አየርን የምትተነፍስ፣ በኢኮኖሚ የጠነከረችና ዘመናዊ የትራንስፖርት ስርዓት ያላት ሀገር ለመሆን ለምታደርገው ጥረት እንደ "ማዕዘን ድንጋይ" የሚቆጠር ነው። ይህ ጅምር ኢትዮጵያን በአፍሪካ የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት አብዮት ውስጥ ቀዳሚ ተምሳሌት ያደርጋታል።</p><p>&nbsp;</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-08T09:49:51+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
