<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://eeu.gov.et/feed/am</id>
                                <link href="https://eeu.gov.et/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://eeu.gov.et/) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-06-30T10:57:02+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[ታዳሽ የሃይል ምንጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ማድረግ ይገባል]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2395?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2395</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>&nbsp;</p><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃ እና ኢነርጂ ሚንስትር እና ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚደርገው የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም (NEP 3.0) ፍኖተ ካርታ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡<br>&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><figure class="image image-style-align-left"><img src="/lfm/1782805850.jpg" alt=""></figure><p>የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ይፋ በተደረገበት ወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ ለአንድ ሀገር እድገት ኢነርጂ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው ታዳሽ የሃይል ምንጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ማድረግ እንደሚገባ አስታውሰዋል።<br>&nbsp;</p><p>በሀገር አቀፍ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚያደርገው ሲሆን በወርልድ ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል። &nbsp;&nbsp;<br>&nbsp;<br>የሀገር አቀፍ የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ዋና ዓላማ በግሪድ ውስጥ እና ከግሪድ ውጪ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሠራ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች እና ከግል ሴክትር ጋር በመቀናጀት አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን እና ማሻሻል እንዲሁም የዲስትሪብዩሽን መሰረተ ልማቶችን ማሳደግ ዋነኛው ተግባሩ መሆኑ ተገልጿል፡፡<br>&nbsp;</p><p>በተጨማሪም የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት ነዋሪዎችን እና የመንግስት ተቋማትን ተጠቃሚ ማድረግ፣ ኤሌክትሪክ ተደራሽ ባልሆኑባቸው አካባቢዎች የሶላር ሲስተምን እና ታዳሽ ኃይል ምንጮችን በመጠቀም ህብረተሰቡን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማደረግ &nbsp;የሚረዳ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>በዚህ ፕሮግራም &nbsp;የግል ሴክተሩ ከግሪድ ውጪ ባሉ አካባቢዎች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማበረታታት፣ በዋናነትም የኤሌክትሪክ ጥራትን ማሻሻል፣ ንጹህ ኢነርጂ እና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እንዲሁም የትምህርት እና የጤና ተቋማትን የኢነርጂ ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡<br>&nbsp;</p><p>በመረሃ ግብሩ በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመው እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈውበታል።<br>&nbsp;</p><p>​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-30T10:57:02+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞቻችን ፣]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/ceo-message/detail/2393?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2393</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image image_resized" style="width:75%;"><img src="/lfm/1782733028.jpg" srcset="/lfm/1782733028.jpg 800w, /lfm/1782733028.jpg 1024w, /lfm/1782733028.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት ጀርባ አጥንት የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ በአስተማማኝ፣ ተደራሽና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማቅረብ ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል። ይሁን እንጂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን መሠረታዊ ፍላጎት ቢሆንም፣ በአጠቃቀም ወቅት በሚፈጠሩ ጥንቃቄ የጎደላቸው ስህተቶችና የደህንነት መመሪያዎችን ባለመከተል ምክንያት ቀላል የማይባሉ የንብረትና የሕይወት ጉዳቶች ሊከሰቱ ይችላሉ።<br>&nbsp;</p><p>​ስለዚህ በቤትዎም ሆነ በሥራ ቦታዎ የኤሌክትሪክ ደህንነትን ማረጋገጥ ምርጫ ሳይሆን የሁላችንም የማይታለፍ ግዴታ ነው ብለን እናምናለን።<br>&nbsp;</p><p>​እንደ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ በምናከናውናቸው የኃይል ማከፋፈልና ጥገና ሥራዎች ሁሉ የሠራተኞቻችንን ብቻ ሳይሆን የክቡራን ደንበኞቻችንን እና የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ዋነኛ ኃላፊነታችን ነው።<br>&nbsp;</p><p>ከዚህም በላይ ደንበኞቻችን በየቤታቸውና በየድርጅቶቻቸው ከኤሌክትሪክ አደጋ ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማስተማርና የማስገንዘብ ሥራዎችን በልዩ ትኩረት እየሠራን እንገኛለን።<br>&nbsp;</p><p>“ቅድሚያ ለደህንነት” የሚለው መርህ በተቋማችን ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ደንበኛችን ቤትና የሥራ ቦታ የእለት ተእለት ባህል መሆን አለበት።<br>&nbsp;</p><p>​ይህንን ግንዛቤ ለማሳደግ ተቋማችን በየሦስት ወሩ የ“የሥራ ላይ ደህንነት ንቅናቄ ሳምንት” በማካሄድ፣ የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆንና የደንበኞቻችንን ደህንነት በላቀ ሁኔታ ለመጠበቅ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል። የዚህ ንቅናቄ ዋና ዓላማ እኛም ሆንን እናንተ ደንበኞቻችን ከትላንቱ በተሻለ ዛሬ ለኤሌክትሪክ ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት እንድንሰጥ ነው።<br>&nbsp;</p><p>​ይህንን ከአደጋ የፀዳ አካባቢ የመፍጠር የጋራ ግብ ለማሳካት፣ እናንተም ክቡራን ደንበኞቻችን በሚከተሉት ነጥቦች ላይ አጋር እንድትሆኑን እንጠይቃለን፦<br>&nbsp;</p><p>• በየቤታችሁና በየድርጅቶቻችሁ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መስመሮችንና ዕቃዎችን በጥንቃቄ መያዝና አደጋ እንዳያደርሱ መከታተል፣</p><p>• ​በአካባቢያችሁ የወደቁ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ወይም አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሲመለከቱ በፍጥነት ለተቋማችን ማሳወቅ፣</p><p>• ​የሚተላለፉ የኤሌክትሪክ ደህንነት የጥንቃቄ መልዕክቶችንና መመሪያዎችን በተግባር ላይ ማዋል፣</p><p>• ​ሕገ-ወጥ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዎችንና ግንኙነቶችን በመከላከል ራስዎንና ቤተሰብዎን መጠበቅ።</p><p>​ቅድሚያ ለደህንነት መስጠት ዛሬን በሰላምና በሕይወት እንድንኖር፣ ነገም በሥራችን ውጤታማ እንድንሆን የሚያስችለን መሠረታዊ ነገር ነው። ማንኛውንም የኤሌክትሪክ መሣሪያ ከመጠቀምዎ በፊት ለደህንነትዎ ቅድሚያ መስጠት የዘወትር ልማድዎ እንዲሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።<br>&nbsp;</p><p>​በመጨረሻም፣ ከአደጋ የፀዳ የኤሌክትሪክ አጠቃቀምን ማረጋገጥ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ፣ ከጎናችን ሆናችሁ አብራችሁን እንድትሠሩ በአክብሮት እጠይቃለሁ።<br><br>​አመሰግናለሁ!<br>&nbsp;</p><p>​ኢንጂነር ጌቱ ገረመው<br>ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት<br>&nbsp;</p><p>​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት<br>#ለደንበኞቻችንደህንነት<br>#ቅድሚያለደህንነት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-29T14:38:12+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
