<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://eeu.gov.et/feed/am</id>
                                <link href="https://eeu.gov.et/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://eeu.gov.et/) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-07-20T15:32:03+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[ትራንስፎርመር ሲሰርቅ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2432?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2432</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>&nbsp;</p><p>በባህር ዳር ሪጅን በአዊ ዞን እንጅባራ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ስር በሚገኘው እንጅባራ ከተማ 02 ቀበሌ ልዩ ቦታው "ዘር ማበጠሪያ ሰፈር" በተባለ አካባቢ፣ ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ ባለ 200 ኪ.ቮ.አ) ትራንስፎርመር በመዝረፍ ላይ የነበረ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተያዘ።<br>&nbsp;</p><figure class="image image-style-align-left"><img src="/lfm/1784550703.jpg"></figure><p>&nbsp;</p><p>ድርጊቱ የተፈጸመው ትናንት ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7፡00 ሰዓት ላይ አካባቢውን ሆን ብሎ ከኤሌክትሪክ ኃይል ውጭ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።<br>&nbsp;</p><p>ይህ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ሲፈፅም የተገኘ ግለሰብ የተያዘው በአካባቢው ማህበረሰብና በጸጥታ ሃይሉ በተደረገ የተቀናጀና ንቁ ክትትል ሲሆን፣ ተጠርጣሪው ግለሰብ የፈታቸውን የትራንስፎርመር ማቴሪያል ጨምሮ በአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።<br>&nbsp;</p><p>በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬና በህዝብ ሃብት የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ መሰል ስርቆቶች ለሃይል መቆራረጥ ዋነኛ መንስኤ እየሆኑ ነው። ድርጊቱ በሃገር፣ በተቋምና በማህበረሰብ ላይ እያደረሰ ያለው ዘርፈ-ብዙ ጉዳት ከቀን ወደ ቀን እየከፋ መምጣቱም ተገልጿል።<br>&nbsp;</p><p>በመሆኑም በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን መከላከልና መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት በመሆኑ፣ በየደረጃው የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል እነዚህን ውድ የልማት አውታሮች እንደ ራሱ ንብረት አድርጎ በንቃት ሊጠብቃቸውና ሊከላከልላቸው እንደሚገባ ተቋሙ ጥሪ ያቀርባል።<br>&nbsp;</p><p>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-20T15:32:03+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[💡 ለአዳዲስ የኤስቲኤስ (STS) ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን እና የኃይል አጠቃቀም📍]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/electrical-tip/detail/2431?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2431</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>#ተቋማችን አስተማማኝና ጥራት ያለው አገልግሎት ለእርስዎ ለማድረስ አዳዲስ የኤስቲኤስ (STS) ቅድመ-ክፍያ ቆጣሪዎችን በስፋት እያገጠመ ይገኛል።<br>&nbsp;</p><p>ይህ ቆጣሪ #የፍጆታዎን መጠን በቀላሉ ለመቆጣጠርና የኃይል አጠቃቀምዎን ለማስተዳደር ትልቅ ዕድል ይሰጥዎታል።<br>&nbsp;</p><p>የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ከሆኑ በኋላ ያልተቋረጠ አገልግሎት እንዲያገኙና የቴክኖሎጂው ሙሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ #የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በጥንቃቄ እንዲተገብሩ በአክብሮት እናሳስባለን፦<br>&nbsp;</p><p>📌 የቅድመ-ክፍያ (STS) ሥርዓት መሆኑን ይረዱ፦ &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>✅ አዲሱ ቆጣሪዎ አገልግሎቱን ከማግኘትዎ በፊት አስቀድመው የሚከፍሉበት (Prepaid) በመሆኑ፣ በቆጣሪዎ ላይ ያለው የገንዘብ/የክፍያ መጠን ሳያልቅብዎ በወቅቱ መሙላትዎን ማረጋገጥ ይኖርብዎታል።<br>&nbsp;</p><p>📌 ድንገተኛ የኃይል መቆራረጥን ያስቀሩ፦<br>&nbsp;</p><p>✅ በቤትዎ ወይም በድርጅትዎ ውስጥ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በሒሳብ ማለቅ ምክንያት ድንገት እንዳይቋረጥብዎ፣ የቆጣሪዎን ቀሪ የፍጆታ መጠን (Balance) ዘወትር ይከታተሉ።<br>&nbsp;</p><p>📌 ወቅቱን የጠበቀ ክፍያ ይፈፅሙ፦<br>&nbsp;</p><p>✅ የፍጆታ ሒሳብዎን ሁልጊዜ በወቅቱ መሙላትዎ አስተማማኝ አገልግሎት ያለማቋረጥ እንዲያገኙ ከማድረጉም በላይ፣ አስፈላጊ ላልሆነ የቅጣት ክፍያዎችን ያስቀራል።<br>&nbsp;</p><p>📌 ቀላልና ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች፦ &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>✅ አዲሱን የSTS ቆጣሪዎን ለመሙላት በአቅራቢያዎ ከሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት በተጨማሪ፣ ያሉበት ቦታ ሆነው በተቋማችን የዲጂታል ክፍያ አማራጮችና የባንክ መተግበሪያዎች (Apps) በመጠቀም በቀላሉ መሙላት ይችላሉ።<br>&nbsp;</p><p>📌 የቴክኖሎጂው ረዳትነት፦<br>&nbsp;</p><p>✅ ይህ ቆጣሪ ፍጆታዎን በራስዎ ፍላጎትና አቅም ልክ ለመቆጠብ የሚያስችልዎ በመሆኑ፣ የወጪዎ ቆጣቢ አድርገው ይረዱት።<br>&nbsp;</p><p>🚫ብርሃንዎን በወቅቱ ክፍያና በዘመናዊው የSTS ቆጣሪዎ ያፅኑ! &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp; &nbsp;</p><p>#SmartMeters<br>#EnergyManagement<br>#EnergyEfficiency<br>#EthiopianElectricUtility</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-20T14:04:27+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[የኤሌክትሪክ አጠቃቀምን ያዘመነው ፤ ዘመናዊው ስማርት ቆጣሪ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/publication/detail/2430?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2430</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (EEU)፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ቀልጣፋና ምቹ አሰራር ለመዘርጋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል። ከተቋሙ ዘመናዊ የአሰራር ማሻሻያዎች መካከል አንዱ እና ዋናው በአገሪቱ እየተተገበረ ያለው የዘመናዊ ስማርት ቆጣሪዎች (Smart Meters) ተከላና ስርጭት ነው። ይህ ስትራቴጂካዊ እርምጃ የኢነርጂ ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገር ባለፈ፣ የአገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ምኞት እውን ለማድረግ ትልቅ አጋዥ ምሰሶ ነው።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን ወደ ላቀ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዓት ለማሸጋገርና በዘርፉ የሚስተዋሉ መዋቅራዊ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችል እጅግ ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክት በአገር አቀፍ ደረጃ በስፋት እየተገበረ ይገኛል። የዩኒፋይድ ፕሪፔይመንት እና ሪቨኑ ፕሮቴክሽን ፕሮጀክት ዋና አካል የሆነው አዲስ አሠራር፥ በመላው አገሪቱ ከ500 ሺህ በላይ ደንበኞችን በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርግ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው።<br>&nbsp;</p><figure class="image image-style-align-left"><img src="/lfm/1784534340.jpg"></figure><p style="text-align:justify;">የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በተመለከተ የፕሮጀክቱ ኃላፊ ወይዘሮ ለምለም ባሳዝነው እንደገለጹት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሩ ተቋሙንና ደንበኛውን በዘመናዊ የመረጃ መረብ የሚያገናኝ ከመሆኑም በላይ፣ ቀደም ሲል በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ በርካታ የአሠራርና የገቢ ስብስብ ክፍተቶችን ሙሉ በሙሉ የማስቀረት አቅም አለው። ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት በስኬት ለማጠናቀቅ ተቋሙ ሰፊ የሎጂስቲክስና የአቅም ግንባታ ዝግጅት አድርጓል። በውሉ መሠረት ኢንሄሜትር (Inhemeter) ከተባለው ታዋቂ የቻይና ኮንትራክተር ጋር በመተባበር 500 ሺህ ቆጣሪዎችን ወደ አገር የማስገባትና 10 ሺህ ቆጣሪዎችን በራሱ በኮንትራክተሩ የመግጠም ሥራ 100 በመቶ በሚባል ደረጃ ተጠናቆ ለሁሉም የሪጅን መዋቅሮች ተሰራጭቷል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በአሁኑ ወቅት ከ 270 ሺህ በላይ የሚሆኑት ቆጣሪዎች በመላው አገሪቱ በሚገኙ ደንበኞች ቤት ላይ ተተክለው ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹንም የማልበስ ሥራ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። የቴክኖሎጂውን ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋፋት ተጨማሪ የ 120 ሺህ ስማርት ነጠላ ፌዝ ቆጣሪዎች ግዥ ተፈጽሞ ወደ አገር የገባ ሲሆን፣ ሌላ ተጨማሪ 400 ሺህ ቆጣሪዎችን ለመግዛት የውል ስምምነት ተፈጽሞ ወደ አገር ለማስገባት በትጋት እየተሠራ ይገኛል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ስማርት ኤ.ኤ.አይ ቆጣሪዎች ቀደም ሲል ተቋሙ በስፋት ሲጠቀምባቸው ከነበሩት መደበኛ የቅድመ ክፍያ (የካርድ) ቆጣሪዎች በብዙ መልኩ የተለዩና የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸው መሣሪያዎች ናቸው። ወ/ሮ ለምለም እንደሚያስረዱት፣ ስማርት ቆጣሪዎች የደንበኞችን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በእውነተኛ ጊዜ (Real-time) የሚቆጣጠሩና መረጃውን በቀጥታ ወደ አገልግሎት ሰጪው ማዕከል የሚልኩ የላቁ ዲጂታል መሣሪያዎች ናቸው። "ይህ ቴክኖሎጂ ቀደም ሲል በነባሮቹ ሜትሮች ሳቢያ በደንበኞች ላይ ይደርሱ የነበሩ በርካታ እንግልቶችን እና የአገልግሎት መቆራረጦችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የተነደፈ ነው። ደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታ ለመግዛት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት መሄድና የሥራ ሰዓትን መጠበቅ ሙሉ በሙሉ ይቀራል፤ ባሉበት ሆነው በማንኛውም ሰዓት መግዛት ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።</p><p style="text-align:justify;"><br>ከዚህም በላይ ቆጣሪው በርካታ የላቁ ባህሪያት ያሉት ሲሆን፣ ደንበኞች በቤታቸው በሚቀመጠው የደንበኛ መገናኛ መሣሪያ (CIU) አማካኝነት የተለያዩ ምስጢራዊ ኮዶችን በመጠቀም የደረሳቸውን የቮልቴጅ መጠን፣ የከረንት መጠን፣ የተፈቀደላቸውን የኃይል መጠንና የሚቀራቸውን የገንዘብ ሂሳብ በቀላሉ መከታተል ይችላሉ። ይህ ግልጽ መረጃ ደንበኞች የኃይል አጠቃቀማቸውን በየሰዓቱ እያዩ እንዲያስተካክሉ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን አመላክተዋል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">እንደ ወ/ሮ ለምለም ማብራሪያ፣ ዘመናዊው አሠራር ከተቋሙ የገቢ ጥበቃና የኃይል ብክነት አኳያ ቀጥተኛና እጅግ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች አሉት። የቅድመ ክፍያ ሥርዓት በመሆኑ ተቋሙ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቅድሚያ እንዲሰበስብ በማድረግ የፋይናንስ አቅሙን ያጠናክራል። ቀደም ሲል በድህረ ክፍያ አሠራር ወቅት በንባብ ስህተት፣ በወቅቱ ባለመክፈልና ሳይሰበሰቡ በሚቀሩ ውዝፍ ዕዳዎች ምክንያት የሚባክነውን ከፍተኛ ገንዘብ ያስቀራል። በተጨማሪም የሰው ኃይልና የተሽከርካሪ ሀብትን በአግባቡ ሥራ ላይ ለማዋል ያስችላል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተጨማሪም ቴክኖሎጂው የላቀ የደህንነት ሥርዓት ስላለው፣ ደንበኞች በሕገ-ወጥ መንገድ ኃይል ለመጠቀም (ስርቆት) በሚሞክሩበት ጊዜ ቆጣሪው ወዲያውኑ ወደ ማዕከላዊ ቢሮ የሪፖርት መልዕክት ይልካል። ከቢሮ ሆኖ ኃይሉን በላቀ የርቀት መቆጣጠሪያ ማቋረጥና መልሶ መቀጠል ማስቻሉ የተቋሙን ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ይጠብቃል። አዲሱ ስማርት ቆጣሪ ቀደም ሲል በድህረ-ክፍያ ሥርዓት ላይ የሚነሱትን ቆጣሪዬ በወቅቱ አልተነበበም፣ “የተጻፈው ንባብ ስህተት ነው ወይም ቤቱ ዝግ ስለነበር ግምት ተሞላብኝ” የሚሉ የደንበኞችን የዓመታት ቅሬታዎች ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በሌላ በኩል፣ ደንበኞች ከተፈቀደላቸው የኃይል መጠን በላይ ሲጠቀሙ የቆጣሪው ውስጣዊ ማስተላለፊያ (Relay) ራሱን በራሱ ስለሚከፍት፣ በትራንስፎርመሮች ላይ ሊፈጠር የሚችለውን የመቃጠል አደጋና የኃይል መቆራረጥን በእጅጉ ይቀንሳል። ይህም የኃይል አቅርቦት ጥራትን በእጅጉ ያሻሽላል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዘመናዊ መሣሪያ በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የፕሮጀክት ቢሮው ሰፊ የኮሙኒኬሽን ስልቶችን ቀርጾ ወደ ስራ ገብቷል። በአገልግሎት ማዕከላት ላሉ ሠራተኞች ተደጋጋሚ ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን፣ በተቋሙ ድረ-ገጽ ላይ በቪዲዮ የተደገፉ ሰፊ ማብራሪያዎች፣ ለማኅበረሰብ ኮሚቴዎች አጫጭር ግንዛቤዎች፣ በኤግዚቢሽኖች ላይ ቀጥተኛ ገለጻዎችና የማስገንዘቢያ ብሮሸሮች ተዘጋጅተው ለደንበኞች እንዲደርሱ መደረጉን አስታውቀዋል ።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ይሁን እንጂ ቆጣሪዎቹ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና የደንበኞችን እርካታ ለመጨመር በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የገዛቸው በመሆናቸው፣ የደንበኞች ኃላፊነትና ጥንቃቄ ወሳኝ ነው። ደንበኞች መረጃዎችን በሙሉ በቤታቸው ባለው የሲ.አይ.ዩ (CIU) መሣሪያ ማየት ስለሚችሉ፣ ዋናውን የውጪ ቆጣሪ በምንም ዓይነት ሁኔታ መነካካት የለባቸውም በማለት አስገንዝበዋል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እየዘረጋው ያለው ዘመናዊ አሰራር የደንበኞችን እርካታ ከማረጋገጡም በላይ አገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለምታደርገው ጉዞ ትልቅ እመርታ ነው። በመሆኑም ህብረተሰቡ የዚህን ዘመናዊ ቆጣሪ ጠቀሜታዎች ተረድቶ፣ የአጠቃቀም መመሪያዎችን በመከተል የኤሌክትሪክ አጠቃቀሙን እንዲያዘምንና ለሀገር ልማት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ይጠበቃል።</p><p>&nbsp;</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-07-20T10:59:37+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
