<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://eeu.gov.et/feed/am</id>
                                <link href="https://eeu.gov.et/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://eeu.gov.et/) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-04-29T11:47:17+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያን በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ደንበኞች የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥ አዲስ የአሰራር ሥረዓት ይፋ ተደረገ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2241?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2241</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያን በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ደንበኞች የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥ አዲስ የአሰራር &nbsp;ስርዓት መዘርጋቱን አስታወቀ።&nbsp;</p><p style="text-align:justify;"><br>ተቋሙ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የአሰራር ሥረዓቱ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት ያልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጿል። &nbsp;&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp; &nbsp;<br>የተቋሙ የማርኬቲንግ፣ ሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር በመግለጫው ላይ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ለማድረግ እና ደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ ዘመናዊ አሰራሮችን እየተገበረ ይገኛል። &nbsp;&nbsp;</p><p style="text-align:justify;"><br>አዲሱ የጊዜ ገደብ ክፍያ ስርዓትም ደንበኞች የማስቀጠያ ክፍያውን እስከ 2 ዓመት በሚደርስ ጊዜ ውስጥ ከወርሃዊ የፍጆታ ክፍያቸው ጋር እንዲከፍሉ የሚያስችል ነው" ብለዋል።&nbsp;</p><p style="text-align:justify;"><br>ይህ አሰራር ተግባራዊ የሚሆነው ለነጠላ ፌዝ (Single Phase) ቆጣሪ አመልካቾች ብቻ ሲሆን፣ደንበኞች ምንም አይነት የማረጋገጫ ሰነድ ማቅረብ ሳይጠበቅባቸው ማመልከቻ በመሙላትና 10 በመቶ ቅድመ ክፍያ በመፈፀም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ። &nbsp;<br>እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ፤ክፍያውን በ6 ወራት ውስጥ ለሚያጠናቅቁ ደንበኞች ምንም አይነት ወለድ የማይታሰብ ሲሆን፣ ከ6 ወር በላይ ለሚጠቀሙ ግን እንደየጊዜው ርዝማኔ ከ3 እስከ 9 በመቶ የወለድ ምጣኔ ይኖረዋል። &nbsp;</p><p style="text-align:justify;"><br>የአሰራር ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ደንበኞች በየወሩ የሚከፍሉት መጠን ከፍጆታ ክፍያቸው ጋር ተደምሮ እንዲቀርብ የሚደረግ መሆኑም ታውቋል።&nbsp;</p><p style="text-align:justify;"><br>የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያውን በአንድ ጊዜ የመክፈል አቅም ያላቸው በአንድ ጊዜ ክፍያ በነባሩ ውል የሚስተናገዱ ሲሆን ሙሉ ክፍያውን በአንድ ጊዜ መክፈል የማይችሉ ደንበኞች ደግሞ በደንበኞቹ ፍላጎት ላይ መሰረት በማድረግ ከፍተኛውን እስከ 24 ወራት ጊዜ (2 ዓመት) በሚቆይ የአከፋፈል ስርዓት ተከፋፍሎ በየወሩ ከወርሃዊ የኢነርጂ ፍጆታ ክፍያቸው ጋር እየተደመረ እንዲከፍሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;"><br>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-29T11:47:17+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ክለቡ በበጀት አመቱ ዓመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለፀ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2240?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2240</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች በአገር አቀፍ በአለም አቀፍ መድረኮች አመርቂ ውጤትን ማስመዝገብ መቻሉን የክለቡ የበላይ ጠባቂ ኢ/ር ጌቱ ገረመው ገለፁ፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ክለቡ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በሂልተን ሆቴል ባካሄደበት ወቅት ኢ/ር ጌቱ እንደተገለፁት በበጀት አመቱ በአገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በተካሄዱ የአትሌቲክስ ውድድሮች ከክለቡ የተመረጡ ሀገርን የወከሉ አትሌቶች አመርቂ ውጤት ማስመዝገባቸው ጠቅሰው በቅርቡ ስፔን ባርሴሎና በሴቶች የማራቶች ውድድር አትሌት ፎቴን ተስፋዬ ያስመዘገበችው በአለም የሴቶች ማራቶን ውድድር ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት እንዲሁም በሀገር ውስጥ በ200 እና በ400 ሜትር አጭር ርቀት ውድድሮች አትሌት መርዶኪዮስ ወልዴ ያስመዘገበው ሪኮርድ ክለቡ እያስመዘገበ ያለው አንፃባራቂ ውጤት ተምሳሌት መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በሌሎች የስፖርት ዘርፎች በእግር ካስ፣ በብስክቴት እና በጠረጴዛ ቴኒስ የሚታዩ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን በማጎልበት ሀገርንና ወገንን የሚያኮራ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">አክለውም ስፖርት ክለቡ በስፖርቱ ዘርፍ በላቀ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲዘልቅ ለማስቻል ከሚከናወነው ስራ ጎን ለጎን አቅም በፈቀደ መጠን ለስፖርቱ አስፈላጊ ግብዓቶችን ማሟላት እንዲሁም ስፖርተኞች ደግሞ ጥቅማ ጥቅሞች እንዲያገኙ የሚያስችል ግልፅ የአሰራር ሂደትን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በዛሬው የክለቡ የጠቅላላ ጉባኤ የክለቡ የ2017 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት አፈፃፀም ለጉባኤው አባላት ቀርበው አስተያየት ተሰጥቶባቸው እና የአባላቱን ድጋፍ አግኝተው ፀድቀዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ አትሌቶች በተገባደደው በጀት አመት በአለም አቀፍ ደረጃ በአሜሪካ ፍሎሪዳ የአለም አገር አቋራጭ ውድድር፣ በፖላንድ በ3000ሜ የቤት ውስጥ ውድድር፣ በአለም ክሮስ ካንትሪ፣ በአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና፣ በባርሴሎና የአለም ማራቶን፣ በናይጄሪያ ካላባር ከተማ በተካሄደ ውድድር፣ በአንጎላ የአለም ወጣቶች ኦሎምፒክ በመሳሰሉ አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በመሳተፉ ሜዳሊያዎችን በማሸነፉ አኩሪ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በሀገር ውስጥም ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገዉ የአለም ግራንድ ፒ ውድድር እንዲሁም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ እና በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ባዘጋጁት ውድድሮች ላይ በመሳተፍና በርካታ ሚዳሊያዎችን በማግኘት አመርቂ ውጤት መስመዝገብ መቻላቸውን ከጉባኤው በቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-29T09:00:34+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኤ.ኤፍ.ዲ ጋር ውይይት አካሔደ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2239?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2239</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፈረንሳዩ ልማት ባንክ ኤ.ኤፍ.ዲ (Agence Française de Développement) ጋር በኤሌክትሪክ ዘርፍ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሰፊ ውይይት አካሔዷል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በውይይቱ ወቅት ሁለቱ ተቋማት በመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት፣ በመሠረተ ልማት ማዘመን፣ በአቅም ማሳደግ እንዲሁም &nbsp;ቴክኖሎጂን በሚመለከት ባንድነት ለመሥራት የሚያስችል አጠቃላይ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ኤ.ኤፍ.ዲ በተለይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአሁኑ ወቅት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራበት የሚገኘውን የኃይል መቆራረጥ ችግርን መቀነስ፣ የኃይል አስተማማኝነትን ማሻሻል፣ የኃይል ብክነትን መቀነስ እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት እንደሚሠራ ተገልጿል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተጨማሪም የሥራ ቦታ ደህንነት ጉዳይ በውይይቱ ላይ ከነበሩ አበይት ጉዳዮች መካከል አንደኛው ነው። ሁለቱ ተቋማት የሠራተኞች ደህንነትን ለማሻሻል የሚያግዙ መመሪያዎችን፣ ስልጠናዎችን እና የቴክኒክ ድጋፎችን በጋራ ለማቅረብ ተስማምተዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ኤ.ኤፍ.ዲ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለተካሔዱ የኃይል መቆራረጥ ጥናቶች የቴክኒክ እገዛ አድርጓል። በቀጣይ ደግሞ በገንዘብ ድጋፍና በቴክኒክ እገዛ ያልተቆራረጠና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለደንበኞች ማድረስ እንዲቻል ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-29T08:58:05+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[የሥራ ደህንነት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://eeu.gov.et/news/detail/2238?lang=am" />
            <id>https://eeu.gov.et/2238</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዓለም አቀፍ የሙያ ደህንነትና ጤንነት ቀን የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከሪጅን ጽ/ቤት የተውጣጡ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተከብሯል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየሁ ሊካሳ ተቋሙ ኤሌክትሪክ የማሠራጨት ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል የሥራ ላይ ደህንነት መሣሪያዎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ &nbsp;<br>&nbsp;<br>ዶ/ር ገበየሁ የሥራ ቦታ ደህንነት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው የኤሌክትሪክ ደህንነት በጣም አስፈላጊና ልዩ ትኩረት የሚሻ ነው ብለዋል፡፡ &nbsp;</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ቀጣይነት ያለው የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች በማከናወን የሚደርሱ የሥራ ላይ አደጋዎችን በመቀነስ አገልግሎት አሰጣጡን ከአደጋ የፀዳ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተያያዘ የተቋሙ የናሽናል ኮኦርዲኔሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ለማ ዓለም አቀፍ የሙያ ደህንነትና ጤና ቀን ሠራተኞች የከፈሉትን ዋጋ ለማሰብ እንዲሁም የሥራ ላይ ደህንነት ባህልን ለመፈተሽ እንደሚከበር ገልፀዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ የሙያ ደህንነትና ጤንነት ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ዳዊት ሰብለወርቅ የተሻለ ልምድ ካላቸው ተቋማት ልምድ በመውሰድ የሴፍቲ ባህልን በማዳበር አደጋውን ለመቀነስ ጥረት ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የዘንድሮ የዓለም የሙያ ደህንነትና ጤንነት ቀን በዓል ስነ-ልቦናዊ እና ጤናማ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ23ኛ ጊዜ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ፤ በተቋሙ ለ6ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-04-29T08:56:38+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
