

<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>http://eeu.gov.et/index.php/feed/am</id>
                                <link href="http://eeu.gov.et/index.php/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://www.eeu.gov.et) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-06-15T16:12:08+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[አዲስ #የኤሌክትሪክ_ቆጣሪ ለማግኘት🔋]]></title>
            <link rel="alternate" href="http://eeu.gov.et/index.php/electrical-tip/detail/2351?lang=am" />
            <id>http://eeu.gov.et/index.php/2351</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image image_resized" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781529079.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781529079.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781529079.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781529079.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p>ማንኛውም ተገልጋይ፤ አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለማግኘት በየደረጃው #የተቀመጡ_መስፈርቶችን በማሟላት ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>🟡 የነጠላ ፌዝ እስከ 7.5 ኪሎ ዋት &nbsp;ሲፈልጉ👇<br>&nbsp;</p><p>📌 ማመልከቻ ወይም ቅጽ መሙላት&nbsp;<br>📌 የፋይዳ መታወቂያ/የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ/ፓስፖርት/መንጃ ፈቃድ (አንዱን)&nbsp;<br>📌 3X4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ&nbsp;<br>📌 አንድ የውል ቴምብር<br>&nbsp;</p><p>🟢 ባለሶስት ፌዝ ከ7.5 ኪሎ ዋት እስከ 25 ኪሎዋት ሲፈልጉ👇</p><p>🔻 ማመልከቻ ወይም ቅጽ መሙላት<br>🔻 የፋይዳ መታወቂያ/የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ/ፓስፖርት/መንጃ ፈቃድ (አንዱን)&nbsp;<br>🔻 3X4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ<br>🔻የውስጥ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ሥራው ደረጃውን ጠብቆ የተከናወነ መሆኑን እና ሀላፊነት የሚወስድ መሆኑን ድርጅቱ ባዘጋጀው ቅጽ ላይ የተፈረመ አባሪ ሰነድ<br>🔻 አንድ የውል ቴምብር<br>&nbsp;</p><p>🔵 ባለሶስት ፌዝ ከ 25 ኪሎ ዋት በላይ ሲፈልጉ👇</p><p>⚡️ ማመልከቻ ወይም ቅጽ መሙላት&nbsp;<br>⚡️ የፋይዳ መታወቂያ/የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ/ፓስፖርት/መንጃ ፈቃድ (አንዱን)&nbsp;<br>⚡️ 3X4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ<br>⚡️ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ<br>⚡️ የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬትና የንግድ ሥራ ፈቃድ ባለው ባለሞያ የተሰራ የኤሌክትሪክ የውስጥ መስመር ዝርጋታ ፕላን&nbsp;<br>⚡️ አንድ የውል ቴምብር፣</p><p>እነዚህን መስፈርቶች ሲያሟሉ ወደ አቅራቢያዎ የሚገኝ #የአገልግሎት_መስጫ_ማዕከላችን በመቅረብ በቀላሉ መስተናገድ ይችላሉ፡፡&nbsp;<br><br>#ቀልጣፋ_አገልግሎት_ለላቀ_ዕርካታ<br>#አዲስ_ቆጣሪ&nbsp;<br>#የኤሌክትሪክ_ተጠቃሚነት<br>#ቀልጣፋ_መስተንግዶ</p><p>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-15T16:12:08+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ሀገርን እየጎዳ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይልና የመሠረተ-ልማት ስርቆት!]]></title>
            <link rel="alternate" href="http://eeu.gov.et/index.php/news/detail/2347?lang=am" />
            <id>http://eeu.gov.et/index.php/2347</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<figure class="image image_resized image-style-align-left" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781509157.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781509157.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781509157.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781509157.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ተደራሽ የኃይል አቅርቦን ለሁሉም ዜጎች ለማድረስ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎችና አዳዲስ አሠራሮችን በሥራ ላይ እያዋለ ይገኛል። በዚህም ሳቢያ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪና መልካም የሆኑ ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን መካድ አይቻልም። ይሁን እንጂ ይህንን ታላቅ ብሔራዊ የልማት ስኬት ወደኋላ የሚጎትትና እንደ ሀገር ትልቅ ስጋት የሆነ አደገኛ ወንጀል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት እየተስተዋለ ነው፤እርሱም በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸም ስርቆትና ውድመት።<br><br>ይህ እኩይ ድርጊት ኅብረተሰቡ ያለምንም መቆራረጥ ማግኘት የሚገባውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳያገኝ ማድረጉ ሳያንስ፣ተቋሙ ሊያገኝ የሚገባውን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት ለኪሳራ እየዳረገው ይገኛል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚፈጸሙ እነዚህ የመሠረተ-ልማት ስርቆቶች በሕዝብና በመንግሥት ሀብት ላይ ትልቅ ምጣኔ-ሀብታዊ ኪሳራ እያስከተሉ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በጀመረችው የልማትና የኢንዱስትሪ ጎዳና ላይም እጅግ አሉታዊና ከባድ ተፅዕኖ እየፈጠሩ ይገኛሉ።<br><br>በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳትና ስርቆት ለመከላከል መንግሥት ጠንከር ያሉ የሕግ ማዕቀፎችን ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወቃል። ለአብነት ያህል የወጣው የኢነርጂ አዋጅ ቁጥር 810/2006 ላይ የተቀመጡት ቅጣቶች የወንጀሉን ከባድነት በግልጽ ያሳያሉ።በኤሌክትሪክ ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ፣ ወይም በሁለቱም ይቀጣል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ማናቸውንም የኤሌክትሪክ ኃይል የሰረቀ፣ &nbsp;በሕገ-ወጥ መንገድ ከሌላ መስመር ያገናኘ፣ ወይም መስመሩ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገናኘ መሆኑን እያወቀ ለፍጆታ ያዋለ ሰው እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 20 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል። የተገጠመለትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ያሰናከለ፣ የኤሌክትሪክ ፍጆታ እንዳይመዘገብ ያደረገ፣ ያለ ይሁንታ መስመር የለወጠ ወይም ምሰሶዎችን የሰረቀ ሰው እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም ከ25 ሺህ ብር ባልበለጠ የገንዘብ መቀጮ ይወሰንበታል።</p><p style="text-align:justify;">በተጨማሪም የቴሌኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት አውታሮችን ለመጠበቅ በወጣው አዋጅ ቁጥር 464/1997 መሠረት፣ በጥፋተኞች ላይ እስከ 10 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚበየን ተደንግጓል። ሆኖም ግን እነዚህ ጥብቅ ሕጎች ቢኖሩም፣ በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆትና ውድመት አሁንም ሊቀንስ አልቻለም።<br><br>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅኖች የሕግ አገልግሎት ድጋፍና አስተባባሪ ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ጌታቸው እንደተናገሩት፣ ተቋሙ በሀገሪቱ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግና ሰፊ አገልግሎት ለመስጠት ብሔራዊ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራሞችንና ሰፊ የመሠረተ-ልማት ዝርጋታዎችን እያከናወነ ይገኛል። ነገር ግን የመሠረተ-ልማት ስርቆት ወንጀል ለሥራው ትልቅ ማነቆና ፈተና መሆኑን ገልጸዋል። ስርቆትና ውድመት እየደረሰባቸው ካሉት ንብረቶች መካከል በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የተገዙ ትራንስፎርመሮች፣ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶች (ኬብሎች) እና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።<br><br>በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ የሚፈጸሙት የስርቆት ወንጀሎች አሳሳቢነት የሚያሳዩ ተጨባጭ መረጃዎች መመዝገባቸውን የገለጹት አቶ ወንድወሰን፣ በ2018 ዓ.ም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የኃይልና የትራንስፎርመር ስርቆት፣ እንዲሁም ለኮሪደር ልማት የተዘረጉ ኬብሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 329 የስርቆት ወንጀሎች ተፈጽመዋል ብለዋል። "በነዚህ የኬብል፣በትራንስፎርመርና በኃይል ስርቆቶች ሳቢያ በተቋሙና በሀገር ላይ የደረሰው የገንዘብ ኪሳራ ከ239 ሚሊዮን 420 ሺህ ብር በላይ ነው" ሲሉ አቶ ወንድወሰን የጉዳቱን መጠን ገልጸዋል።<br><br>እንደ አቶ ወንድወሰን ገለጻ፣ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ስርቆት ማኅበራዊም ኢኮኖሚያዊም ስብራት አለው። ለአብነትም የትራንስፎርመር ክፍሎች፣ የመዳብ ገመዶች እና ሌሎች ቁሳቁሶች ሲሰረቁ የኃይል አቅርቦት በድንገት ይቋረጣል። ይህም የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመጉዳት ባሻገር፣ ተቋማት፣ የሕክምና ማዕከላት፣ ኢንዱስትሪዎች እና የንግድ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ በማድረግ ለትልቅ ምጣኔ-ሀብታዊ ኪሳራ ይዳርጋቸዋል።<br><br>በሌላ በኩል ለስርቆት ተብሎ የሚደረግ ያልተገባ የመስመሮች ንክኪ የእሳት አደጋዎችን ያስከትላል። በተጨማሪም የተመዘበሩና ክፍት ሆነው የሚቀሩ ትራንስፎርመሮች እና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች ሕፃናትን ጨምሮ በንጹኃን ዜጎች ላይ የኤሌክትሪክ ንዝረት አደጋን ይፈጥራሉ። በተቋሙ ላይም ቢሆን መሠረተ-ልማቶችን የመጠገንና ለተጠቃሚዎች የማድረስ ሥራ ላይ መዋል የነበረበት ጠቃሚ ጊዜና ሀብት፣ የተሰረቁትን ለመተካት እንዲውል በመገደዱ የሀገሪቱን የልማት ፍጥነት በእጅጉ ይጎዳል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ምንም እንኳን ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፣ችግሩን በዘላቂነ ለመቅረፍ የመንግሥት የሕግ አስከባሪ አካላት ርምጃ ብቻ በቂ አይሆንም። በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ በሚደርስ ስርቆት ተጎጂው አንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን ሙሉ ሀገራችንና ዜጎቿ መሆናቸው የማይካድ ሐቅ ነው። በመሆኑም ይህ ድርጊት አሁን ካለበት ወደ ከፋ ብሔራዊ ቀውስ ከመድረሱ በፊት፣ እነዚህን የልማት አውታሮች እንደ የገዛ እጅ ሀብት በመቁጠር የመጠበቅና የመከላከል ኃላፊነት የሁላችንም የኅብረተሰቡ፣ የጸጥታ አካላትና የሁሉም ዜጋ ሊሆን ይገባል። የወል ሀብታችንን በጋራ እንጠብቅ!</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-15T10:40:08+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ሀገርን እየጎዳ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይልና የመሠረተ-ልማት ስርቆት!]]></title>
            <link rel="alternate" href="http://eeu.gov.et/index.php/publication/detail/2346?lang=am" />
            <id>http://eeu.gov.et/index.php/2346</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>&nbsp;</p><figure class="image image-style-align-center image_resized" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781508366.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781508366.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781508366.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781508366.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ተደራሽ የኃይል አቅርቦን ለሁሉም ዜጎች ለማድረስ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎችና አዳዲስ አሠራሮችን በሥራ ላይ እያዋለ ይገኛል። በዚህም ሳቢያ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪና መልካም የሆኑ ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን መካድ አይቻልም። ይሁን እንጂ ይህንን ታላቅ ብሔራዊ የልማት ስኬት ወደኋላ የሚጎትትና እንደ ሀገር ትልቅ ስጋት የሆነ አደገኛ ወንጀል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት እየተስተዋለ ነው፤እርሱም በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸም ስርቆትና ውድመት።<br><br>ይህ እኩይ ድርጊት ኅብረተሰቡ ያለምንም መቆራረጥ ማግኘት የሚገባውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳያገኝ ማድረጉ ሳያንስ፣ተቋሙ ሊያገኝ የሚገባውን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት ለኪሳራ እየዳረገው ይገኛል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚፈጸሙ እነዚህ የመሠረተ-ልማት ስርቆቶች በሕዝብና በመንግሥት ሀብት ላይ ትልቅ ምጣኔ-ሀብታዊ ኪሳራ እያስከተሉ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በጀመረችው የልማትና የኢንዱስትሪ ጎዳና ላይም እጅግ አሉታዊና ከባድ ተፅዕኖ እየፈጠሩ ይገኛሉ።<br><br>በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳትና ስርቆት ለመከላከል መንግሥት ጠንከር ያሉ የሕግ ማዕቀፎችን ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወቃል። ለአብነት ያህል የወጣው የኢነርጂ አዋጅ ቁጥር 810/2006 ላይ የተቀመጡት ቅጣቶች የወንጀሉን ከባድነት በግልጽ ያሳያሉ።በኤሌክትሪክ ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ፣ ወይም በሁለቱም ይቀጣል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ማናቸውንም የኤሌክትሪክ ኃይል የሰረቀ፣ &nbsp;በሕገ-ወጥ መንገድ ከሌላ መስመር ያገናኘ፣ ወይም መስመሩ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገናኘ መሆኑን እያወቀ ለፍጆታ ያዋለ ሰው እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 20 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል። የተገጠመለትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ያሰናከለ፣ የኤሌክትሪክ ፍጆታ እንዳይመዘገብ ያደረገ፣ ያለ ይሁንታ መስመር የለወጠ ወይም ምሰሶዎችን የሰረቀ ሰው እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም ከ25 ሺህ ብር ባልበለጠ የገንዘብ መቀጮ ይወሰንበታል።</p><p style="text-align:justify;">በተጨማሪም የቴሌኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት አውታሮችን ለመጠበቅ በወጣው አዋጅ ቁጥር 464/1997 መሠረት፣ በጥፋተኞች ላይ እስከ 10 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚበየን ተደንግጓል። ሆኖም ግን እነዚህ ጥብቅ ሕጎች ቢኖሩም፣ በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆትና ውድመት አሁንም ሊቀንስ አልቻለም።<br><br>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅኖች የሕግ አገልግሎት ድጋፍና አስተባባሪ ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ጌታቸው እንደተናገሩት፣ ተቋሙ በሀገሪቱ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግና ሰፊ አገልግሎት ለመስጠት ብሔራዊ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራሞችንና ሰፊ የመሠረተ-ልማት ዝርጋታዎችን እያከናወነ ይገኛል። ነገር ግን የመሠረተ-ልማት ስርቆት ወንጀል ለሥራው ትልቅ ማነቆና ፈተና መሆኑን ገልጸዋል። ስርቆትና ውድመት እየደረሰባቸው ካሉት ንብረቶች መካከል በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የተገዙ ትራንስፎርመሮች፣ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶች (ኬብሎች) እና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።<br><br>በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ የሚፈጸሙት የስርቆት ወንጀሎች አሳሳቢነት የሚያሳዩ ተጨባጭ መረጃዎች መመዝገባቸውን የገለጹት አቶ ወንድወሰን፣ በ2018 ዓ.ም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የኃይልና የትራንስፎርመር ስርቆት፣ እንዲሁም ለኮሪደር ልማት የተዘረጉ ኬብሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 329 የስርቆት ወንጀሎች ተፈጽመዋል ብለዋል። "በነዚህ የኬብል፣በትራንስፎርመርና በኃይል ስርቆቶች ሳቢያ በተቋሙና በሀገር ላይ የደረሰው የገንዘብ ኪሳራ ከ239 ሚሊዮን 420 ሺህ ብር በላይ ነው" ሲሉ አቶ ወንድወሰን የጉዳቱን መጠን ገልጸዋል።<br><br>እንደ አቶ ወንድወሰን ገለጻ፣ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ስርቆት ማኅበራዊም ኢኮኖሚያዊም ስብራት አለው። ለአብነትም የትራንስፎርመር ክፍሎች፣ የመዳብ ገመዶች እና ሌሎች ቁሳቁሶች ሲሰረቁ የኃይል አቅርቦት በድንገት ይቋረጣል። ይህም የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመጉዳት ባሻገር፣ ተቋማት፣ የሕክምና ማዕከላት፣ ኢንዱስትሪዎች እና የንግድ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ በማድረግ ለትልቅ ምጣኔ-ሀብታዊ ኪሳራ ይዳርጋቸዋል።<br><br>በሌላ በኩል ለስርቆት ተብሎ የሚደረግ ያልተገባ የመስመሮች ንክኪ የእሳት አደጋዎችን ያስከትላል። በተጨማሪም የተመዘበሩና ክፍት ሆነው የሚቀሩ ትራንስፎርመሮች እና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች ሕፃናትን ጨምሮ በንጹኃን ዜጎች ላይ የኤሌክትሪክ ንዝረት አደጋን ይፈጥራሉ። በተቋሙ ላይም ቢሆን መሠረተ-ልማቶችን የመጠገንና ለተጠቃሚዎች የማድረስ ሥራ ላይ መዋል የነበረበት ጠቃሚ ጊዜና ሀብት፣ የተሰረቁትን ለመተካት እንዲውል በመገደዱ የሀገሪቱን የልማት ፍጥነት በእጅጉ ይጎዳል።<br>&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ምንም እንኳን ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፣ችግሩን በዘላቂነ ለመቅረፍ የመንግሥት የሕግ አስከባሪ አካላት ርምጃ ብቻ በቂ አይሆንም። በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ላይ በሚደርስ ስርቆት ተጎጂው አንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን ሙሉ ሀገራችንና ዜጎቿ መሆናቸው የማይካድ ሐቅ ነው። በመሆኑም ይህ ድርጊት አሁን ካለበት ወደ ከፋ ብሔራዊ ቀውስ ከመድረሱ በፊት፣ እነዚህን የልማት አውታሮች እንደ የገዛ እጅ ሀብት በመቁጠር የመጠበቅና የመከላከል ኃላፊነት የሁላችንም የኅብረተሰቡ፣ የጸጥታ አካላትና የሁሉም ዜጋ ሊሆን ይገባል። የወል ሀብታችንን በጋራ እንጠብቅ!</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-15T10:27:45+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
